The News

የአማራ ባሕል ማእከል ግንባታ ፕሮጀክት የአማራ ሕዝብ ባሕሉን፣ ወጉን፣ ጀግንነቱን፣ ሃይማኖቱን፣ ቅርሱን እና ሀገር ሠሪነቱን በቋሚነት የሚዘክርበት ነው" የአልማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መላኩ ፈንታ

Posted on : May: 23/2021

"የአማራ ባሕል ማእከል ግንባታ ፕሮጀክት የአማራ ሕዝብ ባሕሉን፣ ወጉን፣ ጀግንነቱን፣ ሃይማኖቱን፣ ቅርሱን እና ሀገር ሠሪነቱን በቋሚነት የሚዘክርበት ነው" የአልማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መላኩ ፈንታ ባሕር ዳር፡ ግንቦት 15/2013 ዓ.ም (አሚኮ) የአልማ አባላትና ደጋፊዎች ለማእከሉ ግንባታ የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ አማራ ልማት ማኅበር (አልማ) በ1984 ዓ.ም ተመስርቶ በክልሉ ማኅበራዊ ልማትን በመደገፍ የራስን ችግር በራስ የመፍታት አስተሳሰብ አንግቦ እየሠራ የሚገኝ የልማት ማኅበር ነው፡፡ በ2017 ዓ.ም በከፍተኛ ልማታዊ አንድነት የራስን የመልማት ችግሮች በራስ አቅም የሚፈታ ማኅበረሰብ መፍጠር የማኅበሩ ራዕይ ነው፡፡ ማኅበሩ በአማራ ክልል፣ በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ እና በአሶሳ የአባላት አደረጃጀት ዘርግቷል፡፡ በውጪ ሀገ...

Read More

ለአማራ ባህል ማእከል ግንባታ እስካሁን ከ120 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን የአማራ ልማት ማኅበር አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡

Posted on : May: 23/2021

ለአማራ ባህል ማእከል ግንባታ እስካሁን ከ120 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን የአማራ ልማት ማኅበር አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡ ባሕር ዳር፡ ግንቦት 15/2013 ዓ.ም (አሚኮ) ለዘመናት በሀገረ መንግሥት ግንባታ የላቀ ድርሻ ያለውን የአማራ ሕዝብ ባህል፣ ቅርስ፣ እሴት እና ትውፊት የሚገልጽ የባህል ማእከል በአዲስ አበባ አልነበረውም፡፡ በአዲስ አበባ የአማራ ባህል ማእከል ግንባታ ለማካሄድ እንቅስቃሴ ሲካሄድ መቆየቱን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግሥት አገልግሎት ሰጭ ተቋማት አስተባባሪና የአልማ የአዲስ አበባ ከተማ አስተባባሪ አቶ ጃጥራር አባይ ገልጸዋል፡፡ ማእከሉ አብሮነትን እና ኢትዮጵያዊነትን በአዲስ አበባ የምንገነባበት ነው ያሉት አቶ ጃንጥራር በከተማዋ የሚገኙ የአልማ ከ46 ሺህ በላይ አባላት እና ደጋፊዎቹ በማንነታቸው...

Read More

በጎንደርና አካባቢው የአልማ ኮርፖሬት አባላት ምክክር መድረክ ህዝባዊ ተትፎ ለዘላቂ ልማት አልማ 2012-2014 በሚል መሪ ቃል የሚመራውን የለውጥ ዕቅድ ለማሳካት በጋራም ሆነ በተናጥል የድርሻቸውን ለመወጣት እንደሚንቀሳቀሱ የጋራ ውሳኔ አሳለፉ፡፡ የኮርፖሬት አባላቱን የሚያስተባብራቸው ሰባት አባላት ያሉት ኮሚቴ አቋቁመዋል ፤ የሁለት አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች ደረጃ ማሻሻያ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ አስቀምጠዋል፡፡

Posted on : January: 22/2021

አማራ ልማት ማህበር ከሶስት አመታት ወዲህ ትክክለኛ የአማራ ህዝብ የማህበራዊ ልማት ማፋጠኛ ህዝባዊ ማህበር መሆኑን አረጋግጠናል ያሉት የውይይቱ ተሳታፊዎች የነገ አገር ተረካቢ ወጣቶች በአዕምሮ የሚቀረፁባቸው ት/ቤቶች ደረጃቸውን የጠበቁና በቁሳቁስ የተሟሉ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት በጋራም ሆነ በተናጥል ትምህር ተቋማትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ገንብተን እናስረክባለን ብለዋል፡፡ በከተማው ውስጥ ከሚገኙና ደረጃቸውን ካላሟሉ አንጋፋ ት/ቤቶች ውስጥ አንዱ የአፀፄ ፋሲለደስ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የማሻሻያ ግንባታ ዲዛይን በጎንደር ዩኒቨርስቲ በጎ-ፈቃደኛ ምሁራን ተሰርቶ የማሻሻያ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ በክቡር ከናቲባ አቶ ሞላ መልካሙ ነክቡር አቶ መላኩ ፈንታ የአልማ ዋና አስራ አስፈፃሚና በጎንደር ዩኒቨርስቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር አስራት ሀረገ-ወይን ተቀምጧል፡፡ የማሻሻያ ግንባታው...

Read More

የአማራ መገናኛ ብዙሀን ለህዝብ የሚያሰራጫቸው የዜናና ፕሮግራም ዝግጅቶች ለክልሉ ማህበራዊ ልማት መነሻ ሆነው እያገለገሉ መሆኑን የአማራ ልማት ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መላኩ ፈንታ ገለፁ፡፡

Posted on : January: 15/2021

አቶ መላኩ ፈንታ ህዝባዊ ተሳትፎ ለዘላቂ ልማት አልማ 2012-2014 በሚል መነሻ ማህበሩ የሚመራበትን ስትራተጅያዊ የለውጥ ዕቅድ ለብዙሀን መገናኛ ሰራተኞች ባቀረቡበት ወቅት እንደገለፁት ዕቅዱ የክልሉን አጠቃላይ ት/ቤቶች ደረጃ ከሚገኙበት 16 በመቶ ወደ 50 በመቶ ከፍ የማድረግ ዓላማ ቢኖረውም መነሻው የህዝብ ጥያቄና የክልሉ መገናኛ ብዙሀን በየጊዜው በዜናና ፕሮግራም ዝግጅታቸው የሚያደርጉት ጉትጎታ ነው ብለዋል፡፡ የአማራ ብዙሀን መገናኛ ስራዎችና ተቋሙ የሚመራበት የአማራ ክልል ህዝብ ማህበራዊ ለውጥ መሪ ቃል ልማት ማህበራችን ዕቅዱን ከማቀድ ጀምሮ እስከ አፈፃፀም ድረስ ወሳኝ ናቸው ያሉት አቶ መላኩ የተቋሙ ሰራተኞች የልማት ማህበሩ አባል በመሆን ፤የሙያ አስተዋፅኦ በማድረግና እንደተቋምም የፕላትንየም አባል ሆኖ አስተዋፅኦ በማበርክት በዓርያነት የሚጠቀስ ተግባር እያከናወነ መሆ...

Read More

የአማራ ክልል ህዝብ ከምንጊዜውም በላይ በከፍተኛ ፈተና ላይ ቢሆንም እንደ አማራ ልማት ማህበር ዓይነት ህዝባዊ ማህበር በመደራጀትና በትብብር ችግሮችን መሻገር እንደሚቻል የብዙሀን መገናኛ ባለሙያዎች ገለፁ፡፡

Posted on : January: 15/2021

የአማራ ብዙሀን መገናኛ ሰራተኞች የአማራ ልማት ማህበር የ2012-2014 ስትራተጅያዊ የለውጥ ዕቅድ ምክክር መድረክ ላይ እንደገለፁት ሚዲያው ለአማራ ልማት ማህበር ራዕይ እንዲሳካ የሚጥረው የሚዲያ ሽፋን ብቻ ለመስጠት ሳይሆን የአማራ ክልል ህዝቦች በማህበራዊ ልማት የመለወጥና መሻሻል ፍላጎታቸው በዘላቂነት እንዲረጋገጥ ካለው ፅኑ ዕምነትና የዓላማ አንድነት ነው ብለዋል፡፡ ምንም እንኳ ያለፉት አመታት በመንግስት መዋቅራዊ የአሰራር ችግር የአማራ ክልሉ ህዝብ የደረሰበት በደልና አሁንም እየተሻገረ የሚገኘው ፈተና ከፍተኛ ቢሆንም ያለፉ ችግሮች ጎትተው እንዳይጥሉን ትምህርት ወስደን ከአማራ ልማት ማህበር ጎን በመቆም ሁለገብና የተደራጀ ትብብር በመፍጠር የክልሉን ህዝብ ዘላቂ ማህበራዊ ልማት ለማፋጠን ልንሰራ ይገባል ብለዋል የሚዲያ ባለሙያዎች ፡፡ የአማራ ክልል ህዘዝብ ከቀረ...

Read More