The News

በምስራቅ ጎጃም ዞን ማቻከል ወረዳ አልማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አስታወ

Posted on : December: 17/2020

የባሶ ሊበን ወረዳ አልማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በ2012 በጀት አመት ከመደበኛ አባላት ሀብት በማሰባሰብ በደን ቀበሌ በአዲስ ለሚገነባው የደን 2ኛ ደረጃ ት/ቤት1ሚሊዩን 986ሺ99ብር ወጭ በማድረግ 1ብሎክ 4የመማሪያ ክፍሎችያሉት ፣ በየላም ገጅ ቀበሌ ይልማን ቦሴ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት 1ብሎክ 4የመማሪያ ክፍሎች ያሉትና የመምህራን ቢሮ የያዘ በ2ሚሊዩን 389ሺ124 ብር በመገንባባት ከጭቃክፍል ወደ ብሎኬት መቀየር መቻሉን የባሶ ሊበን ወረዳ አልማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አድምቃቸው አሳብ ተናግረዋል ፡፡ አቶ አድምቃቸው አክለውም የማህበረሰቡን ጤና ለመጠበቅ የሚያገለግል በባሶ ሊበል ወረዳ ምችግ ቀበሌ 353ሺ ብር ወጭ በማድረግ ጤና ኬላ መገንባት መቻሉን ገልጸው አማራ ልማት ማህበር በወረዳው እየሰራው ያለውን ስራ በመመልከት የህብረተሰቡ ተነሳሺነት እየጨመረ በመምጣቱ የ2013 ዕቅድን ለ...

Read More

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአዲስ ክፍለ ከተማ አልማ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ።

Posted on : December: 16/2020

በአዲስ አበባ የአዲስ ክፍለ ከተማ አልማ አስተባባሪ አቶ ጀማል መሃመድ እንደተናገሩት የክፍለ ከተማውን ነዋሪዎች በማስተባበር ከ2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የምግብ፣ የአልባሳትና ሌሎች ቁሳቁሶችን የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋ ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ ተደርጓል። ከዚህ በፊት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ ማድረጋቸውን አስተባባሪው ገልጸዋል። በቀጣይም ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነግረውናል። በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የአማራ ክልል ሰራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ሙሉነሽ አበበ የአዲስ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ያደረጉትን ድጋፍ ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎችም ማስቀጠል እንደሚገባቸው ተናግረዋል። የአማራ ክልል አደጋ መከላከል፣ ምግብ ዋስትናና ልዩ ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎች ማስተባበሪያ ኮሚሽን የቅድመ ማስጠንቀቂያና...

Read More

ማህበራዊ ተቋማት ላይ የሚያጋጥሙ የተደራሽነት ችግሮችንና የውስጥ ግብዓት እጥረትን ለመቅረፍ ማህበረሰቡ የአልማ አባል በመሆን የሚጠበቅበትን ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ቀረበ፡፡

Posted on : December: 16/2020

አማራ ልማት ማህበር/አልማ/ ከተቋቋመ ጀምሮ በክልሉ የተለያዩ ተግባራትን በመስራት ለማህበረሰቡ አለኝታነቱን እያሳየ የሚገኝ ማህበር ነው፡፡አልማ ከሚሰራቸው ተግባራት በዋናነት ትምህርትና ጤና ላይ ትኩረቱን በማድረግ የተሻለ የትምህርት ጥራት እንዶኖርና ማህበረሰቡ በአካባቢው የጤና ተቋማት እንዲኖሩት ትምህርት ቤቶችንና ጤና ተቋማትን በመገንባት ማህበረሰቡ ያዋጠውን ገንዘብ መልሶ ለማህበረሰቡ እያስረከበ አግልግሎት እንደሰጡ እያደረገ ነው፡፡ ይህን በማስመልከትም በደብረ ማርቆስ ከተማ አልማ እያከናወናቸው ያሉ ስራዎችንና ሰርቶ ለማህበረሰቡ ያስረከባቸውን ተቋማት አፈፃፀም በማስመልከት እንዲሁም በ2013 በጀት ዓመት ሊያከናውናቸው ባቀዳቸው ተግባራት ዙሪያ ከአባላቱ ጋር በደብረ ማርቆስ ከተማ ውይይት አካሂዷል፡፡ አልማ የተቋቋመበት ዋና አላማ ከማህበረሰቡ ገቢ በመሰብሰብ መልሶ ማህበረሰቡ የሚ...

Read More

አማራ ልማት ማህበር አሜሪካን አገር ከሚገኝና ‘’ ምህረት ሜዲካል ሰፕላይ’’ ከሚባል በጎ ፈቃደኛ ድርጅት ያገኘውን ግምቱ 9.3 ሚሊየን ብር ወጭ የተደረገበት የህክምና ቁሳቁስ ለደጋዳሞት ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት አስረከበ፡፡

Posted on : December: 16/2020

በምክትል ርዕሰ- መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የአማራ ልማት ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር ሙሉነሽ አበበ ለደጋገዳሞት ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ወርቁ ፈንቴ ባስረከቡበት ወቅት እንደገለፁት ጤና ትልቁ የህብረተሰባችን ችግር መሆኑን ጠቅሰው ችግሩን ለመፍታት በዶ/ር ጥላሁን መኮነን ጎሹ የሚመራውና የአካባቢው ተወላጆች ያደረጉት ርበርብ ይህ የህክምና መዳህኒትና ቁሳቁስ ድጋፍ ሊቀርብ ችሏል ብለዋል፡፡ የአማራ ልማት ማህበር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አራጋው ታደሰ በበኩላቸው እያንዳንዱ ሰው አካባቢውን ለማልማት እንደዚሁ ቢነሳሳ አቅም ያላቸው ሰዎች ሊያግዙት እንደሚችሉና ችግሩን ለይቶ ለመፍትሄው ከተረባረበ ከድህነት መውጣት እንደሚቻል ገልፀዋል፡፡ የደጋዳሞት ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ወርቁ ፈንቴ መድሀኒቱንና የህክምና...

Read More

አማራ ልማት ማህበር አሜሪካን አገር ከሚገኝና ‘’ ምህረት ሜዲካል ሰፕላይ’’ ከሚባል በጎ ፈቃደኛ ድርጅት ያገኘውን ግምቱ 9.3 ሚሊየን ብር ወጭ የተደረገበት የህክምና ቁሳቁስ ለደጋዳሞት ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት አስረከበ፡፡

Posted on : December: 16/2020

በምክትል ርዕሰ- መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የአማራ ልማት ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር ሙሉነሽ አበበ ለደጋገዳሞት ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ወርቁ ፈንቴ ባስረከቡበት ወቅት እንደገለፁት ጤና ትልቁ የህብረተሰባችን ችግር መሆኑን ጠቅሰው ችግሩን ለመፍታት በዶ/ር ጥላሁን መኮነን ጎሹ የሚመራውና የአካባቢው ተወላጆች ያደረጉት ርበርብ ይህ የህክምና መዳህኒትና ቁሳቁስ ድጋፍ ሊቀርብ ችሏል ብለዋል፡፡ የአማራ ልማት ማህበር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አራጋው ታደሰ በበኩላቸው እያንዳንዱ ሰው አካባቢውን ለማልማት እንደዚሁ ቢነሳሳ አቅም ያላቸው ሰዎች ሊያግዙት እንደሚችሉና ችግሩን ለይቶ ለመፍትሄው ከተረባረበ ከድህነት መውጣት እንደሚቻል ገልፀዋል፡፡ የደጋዳሞት ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ወርቁ ፈንቴ መድሀኒቱንና የህክም...

Read More