The News

ማህበራዊ ተቋማት ላይ የሚያጋጥሙ የተደራሽነት ችግሮችንና የውስጥ ግብዓት እጥረትን ለመቅረፍ ማህበረሰቡ የአልማ አባል በመሆን የሚጠበቅበትን ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ቀረበ፡፡

Posted on : December: 16/2020

አማራ ልማት ማህበር/አልማ/ ከተቋቋመ ጀምሮ በክልሉ የተለያዩ ተግባራትን በመስራት ለማህበረሰቡ አለኝታነቱን እያሳየ የሚገኝ ማህበር ነው፡፡አልማ ከሚሰራቸው ተግባራት በዋናነት ትምህርትና ጤና ላይ ትኩረቱን በማድረግ የተሻለ የትምህርት ጥራት እንዶኖርና ማህበረሰቡ በአካባቢው የጤና ተቋማት እንዲኖሩት ትምህርት ቤቶችንና ጤና ተቋማትን በመገንባት ማህበረሰቡ ያዋጠውን ገንዘብ መልሶ ለማህበረሰቡ እያስረከበ አግልግሎት እንደሰጡ እያደረገ ነው፡፡ ይህን በማስመልከትም በደብረ ማርቆስ ከተማ አልማ እያከናወናቸው ያሉ ስራዎችንና ሰርቶ ለማህበረሰቡ ያስረከባቸውን ተቋማት አፈፃፀም በማስመልከት እንዲሁም በ2013 በጀት ዓመት ሊያከናውናቸው ባቀዳቸው ተግባራት ዙሪያ ከአባላቱ ጋር በደብረ ማርቆስ ከተማ ውይይት አካሂዷል፡፡ አልማ የተቋቋመበት ዋና አላማ ከማህበረሰቡ ገቢ በመሰብሰብ መልሶ ማህበረሰቡ የሚ...

Read More

አማራ ልማት ማህበር አሜሪካን አገር ከሚገኝና ‘’ ምህረት ሜዲካል ሰፕላይ’’ ከሚባል በጎ ፈቃደኛ ድርጅት ያገኘውን ግምቱ 9.3 ሚሊየን ብር ወጭ የተደረገበት የህክምና ቁሳቁስ ለደጋዳሞት ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት አስረከበ፡፡

Posted on : December: 16/2020

በምክትል ርዕሰ- መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የአማራ ልማት ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር ሙሉነሽ አበበ ለደጋገዳሞት ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ወርቁ ፈንቴ ባስረከቡበት ወቅት እንደገለፁት ጤና ትልቁ የህብረተሰባችን ችግር መሆኑን ጠቅሰው ችግሩን ለመፍታት በዶ/ር ጥላሁን መኮነን ጎሹ የሚመራውና የአካባቢው ተወላጆች ያደረጉት ርበርብ ይህ የህክምና መዳህኒትና ቁሳቁስ ድጋፍ ሊቀርብ ችሏል ብለዋል፡፡ የአማራ ልማት ማህበር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አራጋው ታደሰ በበኩላቸው እያንዳንዱ ሰው አካባቢውን ለማልማት እንደዚሁ ቢነሳሳ አቅም ያላቸው ሰዎች ሊያግዙት እንደሚችሉና ችግሩን ለይቶ ለመፍትሄው ከተረባረበ ከድህነት መውጣት እንደሚቻል ገልፀዋል፡፡ የደጋዳሞት ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ወርቁ ፈንቴ መድሀኒቱንና የህክምና...

Read More

አማራ ልማት ማህበር አሜሪካን አገር ከሚገኝና ‘’ ምህረት ሜዲካል ሰፕላይ’’ ከሚባል በጎ ፈቃደኛ ድርጅት ያገኘውን ግምቱ 9.3 ሚሊየን ብር ወጭ የተደረገበት የህክምና ቁሳቁስ ለደጋዳሞት ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት አስረከበ፡፡

Posted on : December: 16/2020

በምክትል ርዕሰ- መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪና የአማራ ልማት ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር ሙሉነሽ አበበ ለደጋገዳሞት ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ወርቁ ፈንቴ ባስረከቡበት ወቅት እንደገለፁት ጤና ትልቁ የህብረተሰባችን ችግር መሆኑን ጠቅሰው ችግሩን ለመፍታት በዶ/ር ጥላሁን መኮነን ጎሹ የሚመራውና የአካባቢው ተወላጆች ያደረጉት ርበርብ ይህ የህክምና መዳህኒትና ቁሳቁስ ድጋፍ ሊቀርብ ችሏል ብለዋል፡፡ የአማራ ልማት ማህበር ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አራጋው ታደሰ በበኩላቸው እያንዳንዱ ሰው አካባቢውን ለማልማት እንደዚሁ ቢነሳሳ አቅም ያላቸው ሰዎች ሊያግዙት እንደሚችሉና ችግሩን ለይቶ ለመፍትሄው ከተረባረበ ከድህነት መውጣት እንደሚቻል ገልፀዋል፡፡ የደጋዳሞት ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ወርቁ ፈንቴ መድሀኒቱንና የህክም...

Read More

የመተማ ወረዳ አልማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የዲቪኮ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታ አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ማድረጉን አስታወቀ ።

Posted on : December: 16/2020

የመተማ ወረዳ የአማራ ልማት ማህበር ከመደበኛ አባላት በተሰበሰበ 1ሚሊዩን 500ሺ ብር በመተማ ወረዳ ዲቪኮ ቀበሌ የዲቪኮ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት 1 ብሎክ አራት የመማሪያ ክፍሎች ያሉት አዲስ ህንጻ ገንብቶ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ዝግጁ ማድረጉን የመተማ ወረዳ አልማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ እንዳለው ባዘዘው ገልጸዋል ። ኃላፊው አክለውም የዲቪኮ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት በአዲስ የተከፈተ እና በ2012 ዓ.ም እንዲጀምር የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት በፈቀደው መሰረት የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ በማሰብ አማራ ልማት ማህበር በስታንዳርዱ መሰረት ግንባታውን ገንብቶ ማጠናቀቁን እና ለምረቃ ዝግጁ ማድረጋቸውን ተናግረዋል ፡፡

Read More

አማራ ልማት ማህበር የእንቦጭ አረምን ለማጥፋት የሚያገለግል የመዋኛና የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ለጣና ሀይቅና ሌሎች የውሀ አካላት ጥበቃና ልማት መ/ቤት አስረከበ ፡፡

Posted on : December: 15/2020

ድጋፉን ለጣና ሀይቅና ሌሎች የውሀ አካላት ጥበቃና ልማት መ/ቤት ርክክብ ያደረጉት የአልማ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መዝገበ አንዷለም የቁሳቁስ ድጋፉ በጣና ሀይቅ ላይ የተከሰተውን እንቦጭ ለመከላከል የሚያገለግል 300 የዋና ልብስ ፤500 የእጅ ጓንት 56 ካርቶን የገላ ሳሙና በድምሩ 700 ሺ ብር በላይ የሚያወጣ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የእንቦጭ አረምን ለማጥፋት የሚያገለግለው ቁሳቁስ የተገኘው የአልማ በጎ ፈቃደኞችንና ዳያስፖራውን የተቀናጀ አቅም ወደ ልማት የማስገባትና ክልሉን የመደገፍ ፍላጎት ያላቸውን አካላት በማስተባበር ሂደት በአሜሪካ የዲሲ ፤ሜሪላንድና ቨርጅንያ የማህበሩ አባላት መሆናቸውን አቶ መዝገበ ተናግረዋል፡፡ የጣና ሀይቅና ሌሎች የውሀ አካላት ጥበቃና ልማት ተወካይ አቶ ጤናው ምንውየለት የቁሳቁስ ድጋፉን ሲረከቡ እንደገለፁት አልማ በትምህርት ጤናና ስራ እድ...

Read More